ፈልግ

Cookie Policy
The portal Vatican News uses technical or similar cookies to make navigation easier and guarantee the use of the services. Furthermore, technical and analysis cookies from third parties may be used. If you want to know more click here. By closing this banner you consent to the use of cookies.
I AGREE
Finale (Quasi una fantasia) - Andante- Allegro molto
መርዐ-ግብር በድምጽ የቀረበ ዘገባ
ካቶሊኮች በሕፃንነታቸው የሚጠመቁት ለምንድነው? ካቶሊኮች በሕፃንነታቸው የሚጠመቁት ለምንድነው?  (© Antonio Gravante - www.studio-fotograv.com)

ካቶሊኮች በሕፃንነታቸው የሚጠመቁት ለምንድነው?

አንዳንድ ወንጌላውያን ጥምቀት ሰው ክርስቶስን እንደ ግል አዳኙ አድርጎ የመቀበሉ ምልክት የሆነ ምሳሌያዊ መታጠብ ነው የሚል እምነት አላቸው፡፡ በዚህ የእምነት መርህ መሠረት ነፍስ ያላወቀ ሕፃን ኢየሱስን እንደ ግል አዳኙ አድርጎ ለመቀበል ስለማይችል ጥምቀት ዋጋ የለሽ ነው፡፡ ሕፃናትን ማጥመቅ ዋጋ ቢስ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ጥምቀት የግድ አስፈላጊ መሆኑን ኢየሱስ ይናገራል (ዮሐ 3፡5)፡፡

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሁላችንም ከአዳም ኃጢአት ጋር እንደተወለድን እና መጠመቅ እንደሚያስፈልገን ያስተምራል(ሮም 5፡18-19)፡፡ ኢየሱስ በበኩሉ ሕፃናት ወደ እርሱ ሲመጡ መከልከል ተገቢ አለመሆኑን በግልጽ ተናግሯል(ማር10፡14)፡፡ ሐዋርያት በተለያዩ አጋጣሚዎች ሙሉ ቤተሰቦችን አጥምቀዋል(ሐ.ሥ 16፡15፣16፡33፣1ቆሮ 1፡16)፤ እንግዲህ መላ ቤተሰቡ ተጠመቀ ሲባል በዚያ ውስጥ ሕፃናት መኖራቸውን መዘንጋት የለብንም፡፡ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሕፃናት እንዳይጠመቁ የሚያዝ አንድም ዓረፍተ-ነገር አይገኝም

 የቤተክርስቲያን አበው ሕፃናትን የማጥመቅ ሥርዐት በቀጥታ ከሐዋርያት የመጣ መሆኑን ያስተምራሉ፡፡ የሕፃናት ነፍስ አለማወቅ (አለመብሰል፣ ምራቅ አለመዋጥ) በጥምቀት ከሚመሰረተው አዲሱ የኢየሱስ ቃልኪዳን ውጪ ሊያደርጋቸው አይችልም፡፡ በብሉይ ኪዳን ሕፃናት በግዝረት አማካኝነት የእግዚአብሔር የቃልኪዳን ሕዝብ አባል ሲሆኑ እንመለከታለን፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበሩ ወላጆች ልጃቸውን በማስገረዝ ወደ እግዚአብሔር ሕዝብ ቃልኪዳን ይገባ ዘንድ ኃላፊነት እንደሚወስዱ እና ልጁ ነፍስ አውቆ በህፃንነቱ የገባውን ቃል-ኪዳን ደግሞ እስከሚያረጋግጥ በእግዚአብሔር ፊት በእርሱ ፈንታ የእምነት ምሥክሮች ሆነው እንደሚቀርቡ ሁሉ የአዲስ ኪዳን ወላጆችም እንዲሁ በልጆቻቸው ጥምቀት ላይ በእነርሱ ፈንታ የእምነት ምሥክርነት በመስጠት ወደ አዲስ ኪዳን ቃል ያስገቧቸዋል፡፡

01 August 2024, 15:11
Prev
June 2025
SuMoTuWeThFrSa
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
2930     
Next
July 2025
SuMoTuWeThFrSa
  12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
2728293031