ፈልግ

Cookie Policy
The portal Vatican News uses technical or similar cookies to make navigation easier and guarantee the use of the services. Furthermore, technical and analysis cookies from third parties may be used. If you want to know more click here. By closing this banner you consent to the use of cookies.
I AGREE
Allegro vivacissimo - Allegro maestoso assai
መርዐ-ግብር በድምጽ የቀረበ ዘገባ
የአሜሪካ ቢ52 ቦንብ ጣይ አውሮፕላን በሮማኒያ የአሜሪካ ቢ52 ቦንብ ጣይ አውሮፕላን በሮማኒያ   (ANSA)

ቅድስት መንበር በኒውክሌር የጦር መሣሪያዎች ላይ ያላትን 'ጥልቅ ስጋት' ገልጻለች።

በተባበሩት መንግስታት የጄኔቫ ዋና መሥሪያ ቤት በተካሄደው ስብሰባ ላይ ሊቀ ጳጳስ ኤቶሬ ባሌስትሬሮ በኒውክሌር ጦር መሳሪያዎች ስለሚመጣው "ሕልውና ስጋት" አስጠንቅቀዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

በጄኔቫ በተባበሩት መንግስታት የቅድስት መንበር ቋሚ ታዛቢ ሊቀ ጳጳስ ኤቶሬ ባሌስትሬሮ የተባበሩት መንግስታት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ አለመስፋፋት ላይ ለቀረበው ኮሚቴ ንግግር አድርገዋል።

ሊቀ ጳጳሱ ለውይይቱ ለተሰበሰቡት "የ2026 ዓ.ም ሁለተኛው የዝግጅት ኮሚቴ የኑክሌር ጦር መሳሪያ አለመስፋፋት ላይ የተደረገው ስምምነት ሁለተኛ ደረጃ አዘጋጅ ኮሚቴ" በሚል ርዕስ - የቅድስት መንበር የኑክሌር መስፋፋትን በተመለከተ ቅድስት መንበርን "በጥልቅ ያሳሰባት ጉዳይ እንደ ሆነ” ገልጿል።

ለንውክሌር ጦር መሳሪያዎች የሚደርገው ወጪ መጨመር

ሊቀ ጳጳስ ባሌስትሬሮ እንደተናገሩት የኑክሌር ጦር መሳሪያዎች አሁን ባለው “አስጨናቂ ለጦርነት ምቹ የሆነ አካባቢ” እና “በቀጠለው የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ማዘመን እና መስፋፋት” ጉዳይ ላይ ቅድስት መበር እንዳሳሰባት ገልጿል።

በኒውክሌር ጉዳዮች ላይ የቫቲካን ዲፕሎማሲ ልዩ ገጽታ የኑክሌር ጦር መሳሪያ መታጠቅ፣ ለመከላከልም ቢሆን፣ ከሥነ ምግባር አኳያ ስህተት ነው። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በቅርቡ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን የማምረትም ሆነ የማከማቸት ጉዳዮችን በተመለከተ ያላቸውን ስጋት በመግለጽ ሊቀ ጳጳስ ባለስትሬሮ ያሰመሩበት መርሕ ነው።

ሊቀ ጳጳሱ በመቀጠል “ከኑክሌር ጦር መሣሪያ ጋር በተያያዘ የሚደረጉ ወታደራዊ ወጪዎች ቀጣይ ዕድገት” እና “በእዚህ ጉዳይ ላይ የሚደርገው ሰጣ ገባ መጨመር እና ስለ አጠቃቀማቸው ማስፈራሪያዎችን መግለጽ” ቅድስት መንበር ያሳስባታል ብለዋል። እንዲህ ያሉት ድርጊቶች “በአጠቃላይ የሰውን ልጅ ሕልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ ተግባራት ናቸው ሲሉ አክለው ገልጸዋል።

ሶስት ተጨባጭ ሀሳቦች

ሊቀ ጳጳስ ባሌስትሬሮ በመቀጠል ቅድስት መንበር በቀረበው ውይይት ላይ ሦስት ዋና ዋና አስተዋጽኦዎችን ማድረግ እንደምትፈልግ ተናግሯል።

በመጀመሪያ ደረጃ አለመስፋፋት እና ትጥቅ ማስፈታት ከህጋዊ ግዴታዎች በተጨማሪ "ለሁሉም የሰው ቤተሰብ አባላት የስነ-ምግባር ግዴታዎች" መሆናቸውን መገንዘብ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ሊቀ ጳጳስ ባሌስትሬሮ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ እ.ኤ.አ. በ2019 ዓ.ም ናጋሳኪን በጎበኙበት ወቅት እንዳሉት “ሰላምና ዓለም አቀፋዊ መረጋጋት የጋራ ጥፋትን በመፍራት ወይም ሙሉ በሙሉ የመጠፋፋት ስጋት ላይ ለመገንባት ከሚደረገው ጥረት ጋር ተያዞ ተፈጻሚነትን ሊያገኙ አይችሉም።  ሊገኙ የሚችሉት ዓለም አቀፋዊ የአብሮነት እና የትብብር ሥነ-ምግባርን መሰረት በማድረግ ብቻ ነው” ሲሉ መናገራቸውን አስታውሰዋል።

በሁለተኛ ደረጃ፣ ሊቀ ጳጳስ ባሌስትሬሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ክምችት ለመቀነስ ያለመ “ከልብ ውይይት” እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

እናም በመጨረሻም ሊቀ ጳጳሱ ለኒውክሌር ጦር መሳሪያ የሚወጣው ገንዘብ በተሻለ መልኩ ለሰብአዊ ፕሮጀክቶች ሊውል እንደሚችል ጠቁመዋል። በዚህም ምክንያት፣ “ለጦር መሣሪያና ለሌሎች ወታደራዊ ወጪዎች ከሚውለው ገንዘብ የተወሰነው” የሚደግፈው፣ የቅድስት መንበር የረዥም ጊዜ የድህነት ፈንድ ለመመሥረት ያቀረበችውን ሐሳብ በድጋሚ ገልጿል።  

ሊቀ ጳጳስ ባሌስትሬሮ ንግግራቸውን ሲያጠናቅቁ የቅድስት መንበር “ጽኑ እምነት” ከኑክሌር ጦር መሣሪያ የጸዳ ዓለም “የሚቻልም አስፈላጊም ነው” በማለት በድጋሚ አረጋግጠዋል።

 

24 July 2024, 11:35
Prev
June 2025
SuMoTuWeThFrSa
1234567
891011121314
15161718192021
22232425262728
2930     
Next
July 2025
SuMoTuWeThFrSa
  12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
2728293031